Photo credit:tekiva ethiopia
በአዲስ አበባ ቦሌ ዘ ሃብ ሆቴል አካባቢ የእሳት አደጋ ተከሰተ።
አደጋው ከደቂቃዎች በፊት ታምሪን መኪና መሸጫ አካባቢ ዘ ሀብ ሆቴል ፊት ለፊት ባለ አንድ መኖሪያ ቤት መድረሱን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ገልጿል።
አደጋውን በቁጥጥር ሰር ለማዋል የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም የአካባቢው ሰዎች የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ሲሆኑ የእሳት እና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ሰራተኞች በቦታው ደርሰው አደጋውን በቁጥጥር ስር ለማዋል በጥረት ላይ ናቸው።
በሌላ በኩል ፦
በአዲስ አበባ ኡራኤል አካባቢ በመኖርያ ቤቶች ላይ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ደርሷል።
የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በቦሌ ክፍለ ከተማ ኡራኤል አካባቢ በሚገኙ መኖርያ ቤቶች ላይ ድንገተኛ የእሳት አደጋ መድረሱን አስታውቋል።
ባሁኑ ሰአት የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
አደጋው ከደቂቃዎች በፊት ታምሪን መኪና መሸጫ አካባቢ ዘ ሀብ ሆቴል ፊት ለፊት ባለ አንድ መኖሪያ ቤት መድረሱን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ገልጿል።

በሌላ በኩል ፦
በአዲስ አበባ ኡራኤል አካባቢ በመኖርያ ቤቶች ላይ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ደርሷል።
የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በቦሌ ክፍለ ከተማ ኡራኤል አካባቢ በሚገኙ መኖርያ ቤቶች ላይ ድንገተኛ የእሳት አደጋ መድረሱን አስታውቋል።

ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
0 Comments