የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ ገለጸ፡፡

TVs and Audio Category
ከትግራይና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የ12ኛ ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ኤጀንሲው ገልጿል፡፡

ፈተናው በበይነ መረብ (በኦንላይን) እንደሚሰጥ የአገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጄንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ ገልጸዋል፡፡

ለፈተናው የሚያስፈልጉ የግብዓትና የስልጠና ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ዳይሬክተሩ መግለፃቸውን አሃዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።