የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ እና ከፌደራል መሬት ባንክና ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ!
ስምምነቱ በዋናነት የኮርፖሬሽኑን መሰረተ-ልማት ወደ ዲጂታል ስርአት እንዲገባ የማድረግ እና የሳይበር ልማት ስትራቴጂክ ፍኖተ-ካርታ የማዘጋጀት እንዲሁም የመረጃዎቹን ደህንነት ማስጠበቅን የካተተ እንደሆነም ተገልጿል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና የፌደራል መሬት ባንክና ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሌንሳ መኮንን ስምምነቱን ፈርመዋል፡፡

ከኤጀንሲው ጋር የተደረገው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ በቴክኖሎጂ ራሱን ለማዘመን በሚያከውናቸው ስራዎች ላይ ማእከል ያደረገ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በተለይ መረጃን ደህንነቱን ለማስጠበቅ ያለመ ነው ማለታቸውን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት
ዌብሳይታችንን ይጎብኙ

0 Comments