#Axum #Shire


የአክሱምና ሽሬ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ማምሻውን አግኝተዋል 


በትግራይ ክልል በህወኣት ቡድን ጉዳት ደርሶበት የነበረው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠግኖ  የአድዋ፣ አክሱምና ሽሬ ከተሞችና አካባቢያቸው  ዛሬ የኤሌክትሪክ  አገልገሎት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቃል።


Baby products መሠረተ ልማቱን ለመጠገን በተደረገው  ከፍተኛ ጥረት ቀደም ሲል  አብዛኞቹ የትግራይ ኣካባቢዎች የመብራት አገልግሎት ማግኘታቸውንና  የአድዋ ከተማ ደግሞ ዛሬ ከሰዓት በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘቱ ይታወሳል።


በህወኣት ቡድን  ጉዳት ደርሶበት ከጥቅም ውጭ ሆኖ የቆየው  የአክሱምና ሽሬ ከተሞችና አካባቢያቸው  የኤሌክትሪክ መስመር በመጠገኑ  ማምሻውን ከተሞቹ የመብራት አገልገሎት አግኝተዋል።


የሑመራ እና ወልቃይት ከተሞችና አካባቢያቸውን ኤሌክትሪክ ለማገናኘትም  ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።


በዚህ አጋጣሚ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በመሆን የጥገና ስራውን በኋላፊነት ስሜት የተወጡ የተቋሙ ሠራተኞችን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በተቋሙ ሥራ አመራርና ሰራተኞች ስም ማመስገዳቸውን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል።


Baby products